በ’ፊንቴክ’ የማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ቀጠሮ ተሰጠ

Date:

በ”ፊንቴክ” ኢንቨስትመንት ስም በተፈጸመ  የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ታዋቂ አርቲስቶች እና የቲክቶክ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ዛሬ ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

ፍርድ ቤቱ ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፖሊስ ክስ ለመመስረት የሚያስችለውን ምርመራ አጠናቆ እንዲያቀርብ ነበር።

መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን የምርመራ ተግባራት ለችሎቱ በዝርዝር አስረድቷል።

ይሁን እንጂ የወንጀሉ ድርጊት ውስብስብነትና ስፋት ከፍተኛ መሆኑን፤ የተጭበረበረው የገንዘብ መጠንና የተጎጂዎች ቁጥር መበራከቱ ፣ቀሪ ምስክሮችን ለመስማትና የሰነድ ማስረጃዎችን ለማሰባሰብ ጊዜ እንደሚያስፈልገው በመጥቀስ፤ ተጨማሪ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

የተጠርጣሪዎች ጠበቆች በበኩላቸው
ተጠርጣሪዎቹ በሕዝብ ዘንድ የሚታወቁና ቋሚ መኖሪያ ያላቸው በመሆኑ አይሰወሩም፣
ከተጠርጣሪዎቹ መካከል የጤና እክል ያለባቸው ስላሉ በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን ቢከታተሉ፣ የራሳቸው የሆነ መደበኛ መተዳደሪያ ሥራ ያላቸው መሆኑም ታሳቢ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ውሳኔ ለመስጠት ለሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...