ምንም እንኳ ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሐውስ በነበረው የእራት ግብዣ ላይ ስለተፈጠረው ተኩስ እንዲሁም የተጠርጣሪውን መያዝ ብናውቅም አሁንም ያልተመለሱ ጥያቄዎች አሉ።
- ·በአሜሪካ የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ተጠርጣሪው ለፖሊስ የትራምፕ አስተዳደር ሰዎችን ዒላማ ማድረጉን ቢናገርም የሕግ አስከባሪዎች ግን ጥቃቱን ለመፈጸም ያነሳሳው ምክንያት መረጋገጥ አለበት ብለዋል።
- የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ወንጀሉን የፈጸመው ሰው ኮሌ ቶማስ አለን እንደሚባል በመግለጽ ቢዘግቡም ፖሊስ ግን እስካሁን ድረስ በይፋ ስለማንነቱ ያለው ነገር የለም።
- ተጠርጣሪው በርካታ የጦር መሣሪያዎችን መያዙን ፖሊስ ተናግሯል። የተለቀቁ የደህንነት ካሜራ ምስሎች ግለሰቡ የደህንነት ሰዎችን አልፎ ሲሮጥ አሳይተዋል። በእራት ግብዣው ላይ የደህንነት ሁኔታው ምን ያህል የተጠናከረ ነበር የሚለው አሁንም መመለስ ያለበት ጥያቄ ሆኗል።
- የዋይት ሐውስ ዘጋቢዎች የእራት ግብዣ በሚቀጥሉት 30 ቀናት ውስጥ ወደ ሌላ ጊዜ እንደሚተላለፍ ቢገለጽም ቀኑ እስካሁን ድረስ በትክክል አልታወቀም።
