“ከአሜሪካ ጋር መታረቅ የኢሳያስን ፍጻሜ ያፋጥነዋል”

Date:

የቀድሞው የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቲቦር ናጅ፣ የኤርትራን 35ኛ ዓመት የነጻነት በዓል አስመልክቶ ባስተላለፉት መልእክት፣ በፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አስተዳደር ላይ የሰላ ትችት ሰንዝረዋል።

ታላቁ የኤርትራ ህዝብ ለነጻነቱ የከፈለውን መስዋዕትነትና ጽናት ያደነቁት አንጋፋው ዲፕሎማት፣ በሌላ በኩል ግን ዜጎቹን መብት በመንፈግ ሀገሪቱን ወደ ግዙፍ እስር ቤትነት ቀይሯል ያሉትን የአስመራውን አገዛዝ ክፉኛ አውግዘዋል።

ይህ የናጅ ጠንካራ አስተያየት ዋሽንግተንና አስመራ የቆየውን የሻከረ ግንኙነታቸውን ለማደስና ማዕቀቦችን ለማንሳት ፍንጭ እያሳዩ ባሉበት በአሁኑ ወቅት መውጣቱ ደግሞ ጉዳዩን ይበልጥ አነጋጋሪ አድርጎታል።

ዲፕሎማቱ በመልእክታቸው ያልተጠበቀና ስትራቴጂካዊ አንድምታ ያለው የፖለቲካ ትንበያ ያጋሩ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ከአሜሪካ ጋር የተሻለ ግንኙነት ለመፍጠር በራቸውን ክፍት ያደርጋሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ሆኖም ናጅ እንደሚያመለክቱት፣ ይህ ዲፕሎማሲያዊ መቀራረብና ግልጽነት ለኤርትራ መንግስት መረጋጋትን ሳይሆን የአገዛዙን ውድቀት የሚያፋጥን ቀዳዳ ይፈጥራል።

አሜሪካ ከኤርትራ ጋር ግንኙነቷን ብታሻሽል እንኳን፣ የሚመጣው አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ ለኢሳያስ መንግስት መውደቂያ መንገድ ጠራጊ እንደሚሆን በመጠቆም የተለየ የዲፕሎማሲ እይታን አንጸባርቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...