የአፍሪካ ልማት ባንክ 125 ሚሊዮን ዶላር በመመደብ የግል ካፒታልን ለመሳብ አቅዷል

Date:

​የአፍሪካ ልማት ባንክ ለአፍሪካ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ልማት ኢንሹራንስ (ATIDI) የ125 ሚሊዮን ዶላር ካፒታል እንደሚያፈስ አስታወቀ።

ይህ እርምጃ ባንኩ የተቋሙ ትልቁ ባለድርሻ እንዲሆን የሚያደርገው ሲሆን፣ የግል ካፒታልን ወደ አህጉሪቱ ለመሳብ የሚሰጠውን የዋስትና አቅም ለማሳደግ ያለመ ነው።

​ባለፈው መስከረም ወር የባንኩ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ሲዲ ኡልድ ታህ እንደገለጹት፣ ከበለጸጉ አገራት የሚገኘው የልማት ዕርዳታ ባለፈው ዓመት በአንድ አራተኛ ገደማ በመቀነሱ አህጉሪቱ አዲስ የፋይናንስ ሞዴል መከተል አስገድዷታል።

ይህ አዲስ የኢንቨስትመንት ስትራቴጂ “የአፍሪካ አዲስ የልማት ፋይናንስ መዋቅር” (NAFAD) አካል ሲሆን፣ በየዓመቱ የሚታየውን የ400 ቢሊዮን ዶላር የልማት ፋይናንስ ክፍተት ለመሙላት ታስቧል።

እቅዱ በአፍሪካ ውስጥ በተበታተነ መልኩ የሚገኙትን የጡረታ ፈንዶች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች እና የቁጠባ እቅዶችን ጨምሮ 4 ትሪሊዮን ዶላር የሚገመተውን የአገር ውስጥ ካፒታል በቅንጅት ጥቅም ላይ ማዋልን ያለመ ነው።

​በዚህ አዲስ መዋዕለ ንዋይ አማካኝነት የአፍሪካ ልማት ባንክ በኤጀንሲው (ATIDI) ውስጥ ያለው የባለቤትነት ድርሻ ከ3 በመቶ ወደ 14 በመቶ ከፍ ይላል።

ባንኩ በየዓመቱ በተቋሙ በኩል የሚሰጠውን የዋስትና መጠን ወደ 10 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ያቀደ ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል ከነበረው የ3 ቢሊዮን ዶላር አማካይ ዓመታዊ ዋስትና አንጻር ሲታይ የኤጀንሲውን ዓመታዊ የዋስትና መጠን በሦስት እጥፍ ያሳድገዋል ተብሎ ይጠበቃል።

capital

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...