MEXC በድንገት የኢትዮጵያን ብር (ETB) ከP2P ላይ አስወገደ

Date:


ዓለም አቀፉ የክሪፕቶ ምንዛሬ መድረክ የሆነው MEXC የኢትዮጵያ ብርን (ETB) ከP2P ሥርዓቱ ላይ ሙሉ በሙሉ በድንገት ማስወገዱ ተረጋገጠ።

ኩባንያው ቀደም ሲል ይህን አገልግሎት የሚያቆመው እ.ኤ.አ. ሰኔ 30 ቀን 2026 መሆኑን ገልጾ የነበረ ቢሆንም ከተቀመጠው ቀነ-ገደብ ሃያ ቀናት ቀድሞ ውሳኔውን በተግባር አውሏል። በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ብር ምርጫ ከፕላትፎርሙ ላይ ሙሉ በሙሉ ጠፍቷል።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያን የፋይናንስ ህግ መሰረት አድርገው ፦
– ቴሌግራም ዋሌት
– ቢትጌት
– ባይናንስ
– ኦኬኤክስ
– ባይቢት … የመሳሳሉ መድረኮች በኢትዮጵያን ብር የሚደረጉ የክሪፕቶ ግብይቶች (P2P) ማቆማቸው ይታወሳል።

ብሔራዊ ባንክ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ሥርዓት ያለው የዲጂታል ፋይናንስ ተሳትፎ እንዲኖር የሚያስችል አጠቃላይ የቁጥጥር ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ከዓለም አቀፍ አቻ ተቆጣጣሪዎችና ከአገር ውስጥ ባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ መሆኑን መግለጹም ይታወሳል።

@tikvahethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...