የአየር መንገዱ አዲሱ ዘመናዊ አውሮፕላን

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከካናዳው ታዋቂ አውሮፕላን አምራች ዴ ሃቪላንድ ከገዛቸው ሁለት DHC-6 Twin Otter Classic 300-G ዘመናዊ አውሮፕላኖች መካከል የመጀመሪያዋን በይፋ ተረክቧል።

ይህ አዲስና ሁለገብ አውሮፕላን በሀገሪቱ የተለያዩ ክልሎች መካከል ያለውን የትራንስፖርት ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በተለይም ለአስቸጋሪ የአየር ንብረትና አጫጭር የአውሮፕላን ማረፊያ መንገዶች ፍጹም ተመራጭ መሆኑ አየር መንገዱን ይበልጥ ተወዳዳሪ ያደርገዋል።

ይህ ዘመናዊ አውሮፕላን መደበኛ የመንገደኞች በረራን ከማሳለጥ ባለፈ፣ በሀገሪቱ የቱሪዝም እንቅስቃሴ ላይ ትልቅ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።

በተጨማሪም ለአየር ላይ ቅየሳና ጥናቶች እንዲሁም በአስቸኳይ ጊዜ ህይወት አድን አገልግሎት ለሚሰጡ የአየር ላይ አምቡላንሶች የሚውል በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተለያዩ የገበያ ፍላጎቶችን በላቀ ብቃት፣ በታማኝነትና በአስተማማኝ ሁኔታ ለማገልገል ያለውን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነጻነት አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ

በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...