ዜጋዬ ተገድሏል ያለችው ጋና ከደቡብ አፍሪካ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ ውስጥ ገባች

Date:

አንድ ጋናዊ በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ካለው ፀረ ስደተኞች ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ተገደለ መባሉን ተከትሎ በሁለቱ አገራት መካከል ዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ ተቀስቅሷል።

የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዜጋው ኬፕ ታውን ውስጥ በመገደሉ ይፋዊ ተቃውሞውን እና ለፖሊስ አቤቱታ ማቅረቡን ገልጿል።

የደቡብ አፍሪካ የፍትሕ ሚኒስትር ግን “የጋና ባለሥልጣናት መደበኛ ካልሆኑ ስደተኞች ጋር በተያያዘ ባለው ሁኔታ ላይ የሐሰት መረጃዎችን እያስተላለፉ ነው” ሲሉ ተቃውሞ አሰምተዋል።

የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ በበኩሉ ተገደለ ስለተባለው ጋናዊ መረጃ እንደሌለው፤ ነገር ግን ከወንጀል ጋር በተያያዘ ስለተገደለ ሌላ ጋናዊ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አሳውቋል።

የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሥልጣን የሆኑት ክሌይሰን ሞንዬላ ከፀረ ስደተኞች ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ጋናዊ ተገድሏል መባሉን “የፈጠራ ታሪክ ነው” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ጋና በዜጋዋ ላይ የተፈጸመውን ግድያ በመቃወም ባወጣችው መግለጫ “የማንንም ሕይወት መንጠቅ ተቀባይነት የሌለው ድርጊት በመሆኑ ተጠያቂዎቹ በአፋጣኝ ለፍርድ መቅረብ አለባቸው” ስትል ጠይቃለች።

“የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት በግድያው ዙሪያ ፈጻሚዎቹ ተይዘው ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚደያርግ ሙሉ፣ ግልጽ እና ፈጣን ምርመራ እንዲያደርጉ እንፈልጋለን” ብሏል የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ።

የጋና አንድ ሬዲዮ ጣቢያ እንደዘገበው የተገደለው ጋናዊ ለ20 ዓመታት ያህል በደቡብ አፍሪካ ውስጥ የኖረ የልብስ ስፌት ባለሙያ እየነበረ ሲሆን በተቃዋሚዎች በጥይት ተገድሏል። አስከሬኑን ወደ አገሩ ለመውሰድ በጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ጥረት እየተደረገ ነው።

ባለፈው ማክሰኞ ፀረ ስደተኞች ተቃዋሚዎች አፍሪካውያን ስደተኞች ደቡብ አፍሪካን ለቅቀው እንዲወጡ ያስቀመጡት ቀነ ገደብ የነበረ ሲሆን፣ በተለያዩ ከተሞች ውስጥ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል።

ጋና፣ ማላዊ እና ናይጄሪያ ከቀነ ገደቡ በፊት የተወሰኑ ዜጎቻቸውን ከደቡብ አፍሪካ ካስወጡ አገራት መካከል ናቸው። እስካሁን 25 ሺህ የሚደርሱ ሰዎች ደቡብ አፍሪካን ለቅቀው ወጥተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

«የማይናገረው ልዑል» መጽሐፍ በታላቅ ድምቀት ሊመረቅ ነው

ደራሲ መሠረት ክንፈ ኃይሌ ከኦቲዝም ጋር ከሚኖረው ልጇ ልዑል...

በኢትዮጵያ እና በኬንያ ድንበር የሚደረግ ንግድ በገንዘብ መጠን ተገደበ

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኢትዮጵያ እና በኬንያ ድንበር የሚከናወነውን...

(IMF) ከ460 ሚሊዮን ዶላር በላይ ብድር አፀደቀ

አዳዲስ ብድር በመውሰድ ረገድ ጥንቃቄ እንድታደርግ ኢትዮጵያን ያስጠነቀቀው IMF...

ከቡና ኤክስፖርት 3 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ተገኘ

ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት ከቡና ኤክስፖርት 3 ቢሊየን የአሜሪካን...