“ስምምነት ላይ እንደርሳለን አልያም የጀመርነውን እንጨርሳለን”- ትራምፕ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር “ስምምነት ላይ እንደርሳለን አልያም የጀመርነውን ሥራ እንጨርሳለን” ሲሉ አስጠነቀቁ።

ትራምፕ በሰጡት ቃለ ምልልስ የሆርሙዝ ወሽመጥ ቢዘጋም የነዳጅ ዋጋ ብዙም እንዳልጨመረ ተናግረዋል።

“ነዳጅ በብዛት ወስደንባቸዋል። ማንም አላወቀም፤ ይሄ የሆነው በአንድ ወር ተኩል ነው” ብለዋል።

የኢራንን ባሕር ኃይል እና አየር ኃይል ማውደማቸውን በድጋሚ ገልጸዋል።

“መቆጣጠሪያ ሥርዓት እንደሌላቸው አውቀዋል። መቆጣጠሪያ ሥርዓታቸው ስለወደመ በምሽት ዒላማ አድርገናቸዋል” ሲሉም ተናግረዋል።

ትራምፕ “ጉልበተኛው ባሕር ኃይላችን ማንም አይቶት የማያውቅ እገዳ ጥሏል። ለሁለት ወር አንድም መርከብ አላለፈም። ለስምምነት ስንቃረብ እገዳውን አላልተናል። ስምምነት ላይ እንደርስ ይሆናል” ሲሉም አክለዋል።

“ዞሮ ዞሮ እናሸንፋለን። ወይ እንስማማለን ወይም ሥራውን እንጨርሳለን” ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

91 ሚሊዮን የኢራን ሕዝብ “እንዲጎዳ ስለማይፈልጉ” ስምምነት ላይ መድረስን እንደሚመርጡ ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...

እናት ፓርቲ የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን “የእነ አጼ በጉልበቱ መፈንጫ” ሲል ኮነነ ውጤቱንም እንደማይቀበል አስታወቀ

እናት ፓርቲ በቅርቡ የተካሄደውን የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ አጠቃላይ ሂደትና...