አሜሪካ አዲስ ጥቃት ስትከፍት፤ ኤምሬትስ ኢራን በመርከቦቿ ላይ የፈፀመችውን ጥቃት አወገዘች

Date:

የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ኢራን ሰኞ ዕለት በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ በሁለት የነዳጅ ጫኝ መርከቦቼ ላይ ከባድ ጥቃት ፈፅማለች ስትል ኢራንን ከሰሰች።

” አሳፋሪ” ስትል በገለፀችው በዚህ ጥቃት አንድ ሰው የተገደለ ሲሆን ስምንት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱንም ገልጻለች።

ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ዋነኛ መተላለፊያ የመዝጋት እቅዷ አካል አድርገው ሁሉም የንግድ መርከቦች 20% ክፍያ እንዲፈጽሙ እንደሚጠየቁ አስታውቀዋል።

ይህም ደኅንነቱ በተጠበቀ መንገድ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል መተላለፍ እንዲቻል የሚያስፈልገውን ወጪ ለመሸፈን እንደሚውል አክለዋል።

የአሜሪካ ጥቃቶች ለሦስተኛ ቀን የቀጠሉ ሲሆን ፕሬዚደንት ትራምፕ ኢራን ‘በከባዱ’ እንደተመታች ተናግረዋል።

የሁለቱ አገራት ጥቃት ተባብሶ ቀጥሏል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ትራምፕ መተለላፊያው ላይ እገዳ መጣላቸውን ተከትሎ ቴህራን የወሽመጡ “ጠባቂ” ሆና ትቀጥለላች ሲሉ ትራምፕ የተጠቀሙትን ቃል በመጠቀም ምላሽ ሰጥተዋል።

የሆርሙዝ ወሽመጥን ለመቆጣጠር ያለው ውዝግብ የሁለቱን አገራት ጦርነት ለማስቆም ያለውን ጥረት አመንምኖታል።

ሆኖም ትራምፕ አሁንም ቢሆን ስምምነት ማድረግ የሚቻል መሆኑን ገልጸዋል።

ውጥረቱ በቀጠለበት በዚህ ወቅትም ነው የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢራን ክሩዝ ሚሳኤሎች ሁለት የአገሪቷን ታንከሮች ዒላማ ማድረጋቸውን የገለፀችው።

በጥቃቱ አንድ ሕንዳዊ የመርከበኞች ቡድን አባል ሲገደል፣ ስምንት መቁሰላቸውን እና የአራቱ ከባድ ጉዳት መሆኑን ጠቅሳለች።

ከተጎዱት መካከል ስድስቱ ሕንዳውያን ሲሆኑ ሁለቱ ዩክሬናዊያን እንደሆኑ የኤምሬስትስ መከላከያ ሚኒስቴር በኤክስ ገጹ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

“ሚኒስቴሩ ይህንን ዓለም አቀፍ ሕጎች እና ስምምነቶችን በግልጽ የጣሰውን እና በቀጣናው መረጋጋት እና ፀጥታ ላይ ስጋት የደቀነ ጥቃት ያወግዛል” ብሏል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...