በኢትዮጵያ የመነጽር ጥራት ቁጥጥር እጦት ለከፋ የዓይን ችግር እያጋለጠ ነው

Date:

በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ ደረጃ የመነጽርን ጥራት እና ደረጃ የሚቆጣጠር አካል አለመኖሩን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ አስታውቋል ። በዚህም የተነሳ ዜጎች ጥራቱ የተረጋገጠ መነጽር ስለማያገኙ ለከፋ የዓይን ጤና ህመም እየተጋለጡ መሆኑን ተጠቁሟል።

የኮሌጁ የዓይን ህክምና ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ሳዲቅ ታጁ እንደተናገሩት፣ መነጽር በዓይን ጤና ውስጥ እንደ መድሃኒት የሚያገለግል የህክምና ቁስ ቢሆንም፣ ጥራቱንና ደረጃውን የሚለይለት እና የሚቆጣጠርለት አካል በሀገር አቀፍ ደረጃ የለም።

በዚህም ምክንያት ዜጎች ጥራቱ ያልተረጋገጠ ምርት በመግዛት ለተደጋጋሚ ወጪ እና ተጨማሪ የዓይን ችግር እየተጋለጡ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

በተጨማሪም የመነጽር ጥራት ቁጥጥር ባለመኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የመነጽር ቤቶች እና በየመንገዱ መነጽር የሚያዞሩ ግለሰቦች በመብዛታቸው፣ እንዳሻቸው ሰርተውና ዋጋ ተምነው ለተጠቃሚው እያቀረቡ ነው ብለዋል። ይህ ደግሞ ብዙዎችን ለከፋ የዓይን ጤና ችግር እያጋለጠ ነዉ ሲል ኢፕድ ባለሞያውን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል ።

መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆግ መነጽር እንዴት መሰራቱና መገጣጠም እንዳለበት፣ የት ቦታ መሰራቱ እንዳለበት፣ በምን ያህል የጥራት ደረጃ መሰራቱ እንዳለበት፣ በምን አይነት መልኩ መሸጥ እንዳለበት የሚሉትን ጉዳዮች ለይቶ የሚሰራ አካል መመደብና አፈጻጸሙን መቆጣጠር ያስፈልጋል ተብሏል።

Source: capitalethiopia

ቀዳሚ ጽሑፍ
ቀጣይ ጥሑፍ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...