በጎርጎሮሳውያኑ 2024 በኢትዮጵያ 43 ጋዜጠኞች ለእገታ እና እስር መዳረጋቸውን ሪፖርት አመለከተ

Date:

የጋዜጠኞች ደህንነት ግምገማ በማካሄድ የሚታወቀው አለም አቀፉ የሚዲያ ድጋፍ ተቋም ባወጣው ሪፖርት በኢትዮጵያ በጎርጎሮሳውያኑ 2024 ብቻ 43 ጋዜጠኞች ለእገታ እና እስር መዳረጋቸውን አስታወቀ። ሪፖርቱ ጋዜጠኞች ከመንግስት እና መንግስትዊ ካልሆኑ አካላት ማስፈራሪያ፣ እስር እና እንግልትን ጨምሮ ለበርካታ ጫናዎች ተጋላጭ መሆናቸውን አመላክቷል።

ከ60 ጋዜጠኞች ጋር በተደረገ ቃለ መጠይቅ እና በሰነድ በተመዘገቡ ጉዳዮች ላይ የተመሠረተው ሪፖርቱ፣ በግጭት በተጎዱ አካባቢዎች ያሉ ጋዜጠኞች በተለይም በ አማራ፣ ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ከፍተኛ አደጋ እንደሚገጥሟቸው አረጋግጧል።

በሪፖርቱ መሠረትም “የታጠቁ ቡድኖች ጋዜጠኞችን የቤዛ ክፍያ ለመቀበል ወይም ስለግጭቶች የሚወጡትን የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎችን ለመቆጣጠር እንዲሁም ቁሳቁሶቻቸውን ለመወሰድ በማሰብ በዘፈቀደ አስረዋል።  በሌላ በኩል የመንግስት ባለሥልጣናት ደግሞ “ብሔራዊ ደህንነት እና ብሔራዊ ጥቅም” በሚል ሰበስ ጋዜጠኞች እንዲታሰሩ ማድረጋቸውን ሪፖርቱ አመላክቷል።

@ አዲስ ስታንዳርድ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...