በኢትዮጵያ 3.8 ሚልየን ዓመታት እድሜን ያስቆጠረ የራስ ቅል መገኘቱ ተገለፀ

Date:

በኢትዮጵያ 3.8 ሚልየን ዓመታት ዕድሜን ያስቆጠረ የኦስትራሎፒቴከስ አናሜንሲስ ዝርያ የኾነ የራስ ቅል መገኘቱ ተገለፀ። በአፋር ክልል ሚሌ አካባቢ መገኘቱ የተገለፀው ቅሪት አካል በዓለም አቀፍ አንትሮፖሎጂስቶች ቡድን የካቲት 2008 ዓ.ም. እንደተገኘ ማወቅ ተችሏል። የተገኘው የራስ ቅል ከዘመናዊ የሰው ልጅ ጋር ተዛማጅነት ካላቸው ቀደምት የኦስትራሎፒተከስ ዝርያዎች አንዱ የሆነው የኦስትራሎፒቲከስ አናሜንሲስ እንደኾነም ተነግሯል። ኦስትራሎፒቲከስ አናሜንሲስ ከዚህ ቀደም የሚታወቀው በመንጋጋ አጥንቶች፣ በተቆራረጡ ጥርሶች እና ጥቂት በተሰበሩ የእጅ አጥንቶች ሲኾን ይህ በተመራማሪዎቹ የተገኘው የራስ ቅል ሙሉ በመኾኑ የአውስትሮሎፒቲከስ አናሜንሲስ ዝርያ ምን እንደሚመስል ለማወቅ እንደሚረዳቸው እምነት ተጥሎበታል። የአውስትራሎፒትከስ አፋርነሲስ ዝርያ የኾነችው ሊሲ (ድንቅነሽ) በአፋር ክልል ሃዳር አካባቢ በፈረንጆች 1974 እንደተገኘች ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...