በትግራይ ክልል 1.2 ሚሊየን ልጆች ወደ ትምህርት ገበታ አልተመለሱም

Date:

በትግራይ ክልል 1.2 ሚልዮን ሕፃናት እና አዳጊ ልጆች ወደ ትምህርት ገበታ አለመመለሳቸው ተገለጸ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንደገለጸው በትግራይ ከጦርነቱ በኋላ ጭምር የቀጠለው ሰብአዊ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር ሚልዮኖች ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ አድርጓል።

በዚህም ላይ እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የተፈናቃዮች ጉዳይ ሌላው ልጆች ትምህርት ቤት እንዳይ ሄዱ እንቅፋት እንደሆነም ተገልጿል።

በዚህ ዓመት በትግራይ ክልል 2.5 ሚልዮን ተማሪዎች ነበሩ ወደ ትምህርት ቤት ይገባሉ ተብሎ የታሰበው፤ ሆኖም አሁን በትምህርት ገበታ ላይ የሚገኙት 1.3 ሚልዮን ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሐላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዑሽ ተናግረዋል።

ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ ተማሪዎች ቁጥር ከመቀነሱ ጎን ለጎን የትምህርት ጥራቱ ላይም ክፍተት እየተስተዋለ መሆኑ ተነግሯል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...