3ኛው ኢንቨስት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው

Date:

የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድል ለማስተዋወቅ ያለመው 3ኛው ኢንቨስት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም ከግንቦት 4 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል።

ይህ ፎረም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን (ኢኢኮ)፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በልማት አጋር ድርጅቶች ትብብር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፣ ፎረሙ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ፣ መንግስት ለዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ትኩረት እና አዳዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ለማስተዋወቅ እንደሚረዳ አመልክተዋል።

ባለፈው ዓመት በተካሄደው 2ኛው የኢንቨስት ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም ከ750 በላይ ድርጅቶች መሳተፋቸውንና ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት ለማድረግ ቃል የተገባበት እንደነበር አስታውቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...