3ኛው ኢንቨስት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው

Date:

የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድል ለማስተዋወቅ ያለመው 3ኛው ኢንቨስት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም ከግንቦት 4 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል።

ይህ ፎረም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን (ኢኢኮ)፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በልማት አጋር ድርጅቶች ትብብር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፣ ፎረሙ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ፣ መንግስት ለዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ትኩረት እና አዳዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ለማስተዋወቅ እንደሚረዳ አመልክተዋል።

ባለፈው ዓመት በተካሄደው 2ኛው የኢንቨስት ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም ከ750 በላይ ድርጅቶች መሳተፋቸውንና ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት ለማድረግ ቃል የተገባበት እንደነበር አስታውቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...