10ኛው የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነዉ

Date:

(ሚያዝያ 13/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ 10ኛዉን ከተማ አቀፍ የሳይንስ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ከሚያዚያ 16-18/2017 ዓ.ም ድረስ “በፈጠራ ስራ የተካነ ትጉህ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና!” በሚል መሪ ሀሳብ ከፍተኛ የመንግስት የሰራ ሀላፊዎች ፣ የትምህርት አመራሮች ፣ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ፣ የትምህርት ባለሙያዎች ፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት በወዳጅነት ፓርክ ያከናውናል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ እያከናወናቸው ያሉ የትምህርት ልማት ስራዎች ፍራቸውን በሳይንስና የፈጠራ ስራ ላይ የምናይበት ብሎም በዓውደ ርዕዩ ላይ የምንመለከታቸው የተማሪዎችና የመምህራን የፈጠራ ስራዎች የሀገራችንን የፈጠራ ስራ ወደ ፊት ከፍ የሚያደርጉ እንደሚሆኑ ይታመናል፡፡

10ኛዉን ከተማ አቀፍ የሳይንስ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ለትውልድ ግንባታ የተሰጠውን የላቀ ትኩረት በተጨባጭ በፈጠራ ስራው ከፍ ብሎ በተግባር የሚታይበት ፤ ችግር ፈቺ ትጉ ትውልድ የሚገነባበትና ለአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልጽግና የሚሰሩ ጥበበኛ ወጣቶችን የምናይበት መድረክ እንደሚሆንም ይጠበቃል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...