በኬንያ የኃይል ፍላጎት የጨመረ ሲሆን ሊያጋጥም የሚችልን የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ለማስገባት እንዳቀደች ተነግሯል።
የኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ጆሴፍ ሲሮር ከኢትዮጵያ ተጨማሪ ከ50-100 ሜጋ ዋት ኃይል ለማስገባት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ንግግር ስለመጀመሩ ገልፀዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው አሁን የተጠየቀው ጥያቄ እስካሁን እየገባ ካለው የ200 ሜጋ ዋት በተጨማሪ መሆኑን ሲገልፁ ኃይሉ የተፈለገው ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ባለበት ከምሽት 12 ሰዓት እስከ ምሽት 4 ሰዓት ድረስ መሆኑን ገልፀዋል።
በ2024 የኬንያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደገለፀው ኬንያውያን ከሚጠቀሙት ዕለታዊ የኃይል ፍጆታ ውስጥ 11 በመቶው ከኢትዮጵያ እንደነበር መግለፁ ይታወሳል።
ኬንያ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኡጋንዳ እና ከታንዛኒያ ታስገባለች።
@tikvahethmagazine
