እናት ፓርቲ፣ በተያዘው ዓመት የመንግሥት የድጋፍ ገንዘብ እንደማያገኝ ምርጫ ቦርድ በደብዳቤ እንዳሳወቀው ገልጧል። ቦርዱ ፓርቲው የገንዘብ ድጋፍ እንዳያገኝ የወሰነው፣ ባለፈው ዓመት የተሠጠውን የገንዘብ ድጋፍ “ከታለመለት ዓላማና ተግባር ውጭ” ተጠቅሞበታል በማለት እንደሆነ ፓርቲው ጠቅሷል። ቦርዱ፣ የፓርቲውን ፕሬዝዳንት ጨምሮ የድጋፍ ገንዘቡ ከታለመለት ዓላማ ውጪ እንዲውል አድርገዋል ባላቸው ሦስት አመራሮቹ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ እንዲያደርግ መጠየቁንም በደብዳቤው ላይ እንደገለጠ ፓርቲው አስታውቋል። ፓርቲው፣ የቦርዱ ውሳኔ “ፖለቲካዊ ግብ ያዘለ ነው” በማለት ተችቷል።
