ኢትዮጵያ ከቡና የውጪ ንግድ በሀገሪቱ ታሪክ ከፍተኛውን ገቢ ሰበሰበች

Date:

በበጀት ዓመቱ 10 ወራት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ የቡና ኤክስፖርት አፈጻጸም መመዝገቡን የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

ሀገሪቱ በ10 ወራት ውስጥ ከቡና ብቻ ከ1 ነጥብ 8 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ላይ ገቢ ማግኘቷንም የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ ባለስልጣኑ በበጀት ዓመቱ 10 ወራት 354 ሺህ 302 ቶን ቡና ወደ ውጭ መላኩን ጠቁመዋል፡፡

ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በመጠን የ145 ሺህ 316 ሺህ ቶን፣ በገቢ ደግሞ የ869 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ እንዳለው አስታውቀዋል፡፡

በ10 ወራት የኢትየጵያ ቡና ቀዳሚ መዳረሻ ሀገራትም በቅደም ተከተል ጀርመን፣ ሳዑዲ አረቢያ እናአሜሪካ እንደነበሩም አስታውሰዋል፡፡

ለተመዘገበው ስኬት ከመንግስት ጋር በቅንጅት ርብርብ ላደረጉ አካላትም ዋና ዳይሬክተሩ ምስጋና ማቅረባቸውን ከባለስልጣኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...