በተባበሩት መንግስታት ስር ያሉ ተቋማት የግዢ ጨረታ የአዲስ አበባ የንግዱ ህብረተሰብ ጥሪ ቀረበ

Date:

በኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ስር የሚንቀሳቀሱ 29 ተቋማት እንዳሉም መረጃዎች ያሣያሉ ተቋማቶቹ በሚያወጡት የግዢ ጨረታ በከተማው የሚገኙ ነጋዴዎች ተሳታፊ መሆን ይጠበቅባቸዋል ፡፡

የአዲስ ቻምበር ተጠባባቂ ዋና ፀሐፊ አቶ ዘካሪያስ አሰፋ በሴሚናሩ ላይ እንደገለጹት የተባበሩት መንግስታት በሚያወጣቸው የአገልግሎትና የእቃዎች ግዢና ጨረታ የአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ህብረተሰብ ይበልጥ ተሳታፊ እና ተወዳዳሪ እንዲሆን ቻምበሩ እየሰራ ይገኛል ፡፡

የንግዱ ሕብረተሰብም ተወዳዳሪ እንዲሆን የአቅም ግንባታ ስራዎች ንግድ ምክር ቤቱ ከተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን ያከናወናል ብለዋል።

ቻምበሩ በኮሚሽኑም ሆነ በሌሎች የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች የሚወጡ የግዢ ፍላጎቶች የንግዱ ህብረተሰብ ተሳታፊና አቅራቢ የሚሆንበትን ሁኔታ ይፈጠራል ብለዋል ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...