ጎተራ አካባቢ ሊፈርስ መሆኑ ተሰማ

Date:


በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ውስጥ የሚገኘውና ጎተራ ተብሎ የሚጠራው ሰፈር ሊፈርስ መሆኑን ዘሪፖርተር እንግሊዘኛ ጋዜጣ ትናንት ባቀረበው ዘገባ አስታውቋል፡፡

‹‹አዲስ ቱሞሮው›› በሚል ፕሮጀክት የከተማው አስተዳደር ለሚያስገነባው ልዩ የኢኮኖሚ መንደር አካባቢውን ለማፍረስ መታቀዱንም አስረድቷል፡፡

ፕሮጀክቱ በአዲስ አበባ ከንነቲባ አዳነች አቤቤና በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የሚመራ እንደሆነ የጠቀሰው ዘገባው የከተማው አስተዳደር መንደሩን ለመገንባት ከቻይናው የኮሚኒኬሽንና ኮንትራክሽን ድርጅት ጋር ስምምነት መፈፀሙን አስታውቋል፡፡

መንደሩ የንግድ፣ የፋይናንስ፣ የትምህርት፣ የባህልና ሰማይ ጠቀስ የመኖሪያ ህንፃዎች እንደሚኖሩት መገለፁን ያስረዳው ዘገባው በመሆኑም በጎተራ አካባቢ በሚገኝ ሰፊ መሬት ላይ ለመስራት እንደታሰበ ጠቅሷል፡፡

የአዲስ ቱሞሮው መንደር ግንባታ በቢሊዮን የሚቆጠር ብር እንደሚፈጅ አስረድቶም ከዚህም በላይ በጎተራ አካባቢ የሚኖሩ በርካቶችን እንዲፈናቀሉ እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡

በአሁኑ ወቅት በኮሪደር ልማትና በጫካ ፕሮጀክት ፕሮጀክቶች አማካኝነት በመቶ ሺ የሚቆጠሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ተፈናቅለው ወደተለያዩ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ የተደረገ ሲሆን በዚህኛው ፕሮጀክትም በርካታ ነዋሪዎች ተመሳሳይ እጣ እንደሚገጥማቸውም አስታውቋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...