ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ለሚሰነዘርባት ዘለፋ ምላሽ የመስጠት ፍላጎት የላትም ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ

Date:

ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት ከጎረቤት ሀገራት ለሚሰነዘርባት ዘለፋዎች ምላሽ የመስጠት ፍላጎት የላትም ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ ዛሬ ግንቦት 21 2017 ዓ.ም በወቅታዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረውን ሳምንታዊ መግለጫ፤ በቃል አቀባዩ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በኩል ሰጥቷል።

ቃል አቀባዩ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሁልጊዜም የተሻለ ግንኙነት ለመፍጠር እንደምትሰራ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።

ከሰሞኑ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኤርትራን የነፃነት ቀን ግንቦት 16 ባከበሩበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያን በተመለከተ ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል።

ይህ ንግግራቸው በርካታ ኢትዮጵያዊያንን ያስቆጣ ሲሆን፤ የተለያዩ ሀሳቦችም እየተሰነዘሩበት ቆይተዋል።

ይህንን በተመለከት ጥያቄ የቀረበለት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ በቃል አቀባዩ በኩል ምላሽ የሰጠ ሲሆን፤ ቃል አቀባዩ “ኢትይዮጵያ ለሚሰነዘሩባት ዘለፋዋች ምላሽ የምስጠት ፍላጎት የላትም” ብለዋል።

ኢትዮጵያ የተረጋጋ አካሄድን የምተከተል ሀገር መሆኗን የገለጹት አምባሳደር ነብያት፤ “ከዚህ ቀደምም ከሌሎች ጎረቤት ሀገራት በመሪዎቹ ደረጃ ተገቢ ያልሆኑ ክሶችና ዘለፋዋች ደርሶባት ያውቃል” ሲሉ ገልጸዋል።

“ኢትይጵያ ግን እንደዚህ ያለ እንካ ሰላምትያ ዉስጥ ሳተገባ በሰከነ ዲፕሎማሲ መንገድ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የምትቀጥል ነው የሚሆነው” ብለዋል።

በሌላ በኩል የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሥም በመጠቀም ‘ወደ ውጪ እንልካለን’ የሚሉ አካላት መኖራቸውንም የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቋል

ከዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ጋር በተያያዘ ከማይናማር ከ700 በላይ ዜጎችን መመለስ መቻሉንም አምባሳደሩ በሳምንታዊ መግለጫቸው ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ መንግሥት በዚሁ ሁሉ ጥረት እያደረገ ባለበት በዚህም ወቅት፤ ይህንን የሕገ-ወጥ መንገድ ተከትሎ የሚሄዱ ዜጎች አሁንም መኖራቸውን እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል።

‘ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕጋዊ ፍቃድ አለኝ’ በማለትና የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሥም በመጠቀም ሀሰተኛ ማስረጃ በማስራጨት ‘ወደ ውጪ እልካለሁ’ የሚሉ ሐሰተኛ ግለሰቦች መኖራቸውን ሕዝብ ሊረዳ ይገባል ብለዋል።

ይህ ሀሰተኛ ማስረጃ በተለያየ ማህበራዊ ሚዲዎች እየተሰራጨ መሆኑን የገለጹት አምባሳደሩ፤ ስህተት መሆኑን ሕዝብ ሊረዳ እንደሚገባም አሳስበዋል።

“የሕገ-ወጥ መንገድ የሚወስዱ ደላሎች ሰንሰለታቸው ረጅም ርቀት ያለው ቢሆንም፤ ርምጃ ለመውሰድ ሥራዎች ቢሰሩም አሁንም ችግሩ አልተቀረፈም” ሲሉም ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...