አፍሪኤግዚም ባንክ ለኢትዮጵያ የንግድ ማሕበረሰብ ድጋፍ

Date:

የባንኩ የምሥራቅ አፍሪካ ክልላዊ ጽሕፈት ቤት ግንቦት 25 እና 26 “የኢትዮጵያን ዕድገት መደገፍ፡ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪያላይዜሽንን በአፍሪኤግዚም ባንክ መፍትሄዎች ማነቃቃት” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ትርዒት ለማካሄድ አቅዷል።

ባንኩ ባለፉት አምስት ዓመታት በንግድ ፋሲሊቴሽን ፕሮግራሙ ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ የተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት 4 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር የሚገመት የንግድ ልውውጥ ማመቻቸቱን ገልጿል።

በ2024 የኢትዮጵያ ኩባንያዎች በባንኩ የንግድ ክፍያ አገልግሎቶች ፕሮግራም 32 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ግምት ያላቸውን ዓለም አቀፍ የንግድ ክፍያዎች ፈፅመዋል።

53 የአፍሪካ ሀገራትን በአባልነት ያቀፈው ባንኩ ከኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ባለፈ ከሀገሪቱ የንግድ ማሕበረሰብ ጋር የላቀ ግኑኝነት ለመፍጠር እንዳቀደ ገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ካናዳ ምዝገባም ሆነ ስምሪት አልተጀመረም

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል"...

የክቡር ዶክተር ጋሽ መሐሙድ አዲስ አልበም ለአድማጮች ሊደርስ ነዉ

ታዋቂው ድምፃዊ ክቡር ዶክተር አርቲስት መሐሙድ አሕመድ «ለታሪክ» የተሰኘውንና...

ሜታ ‘ፌስቡክ እና ኢንስታግራም በቀረበባቸው ክስ 18 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል ተስማማ

ግዙፉ የማኅበራዊ ሚዲያ ኩባንያ ሜታ በፌስቡክ እና በኢንስታግራም ምክንያት...