ኢትዮጵያዊቷ ቆንጆ ከአፍሪካ 1ኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቀቀች

Date:

በህንድ እየተከናወነ ያለው ሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር አሁን ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ በዚህ ውድድር የ109 አገራት ቆነጃጅት የተሳተፉ ሲሆን ‹‹ሚስ ወርልድ›› የሚል መጠሪያ በማግኘት የዘንድሮውን ዘውድ የጫነችው ታይላንዳዊቷ ኦፓል ሱቻታ ሆናለች፡፡

እሷን ተከትላ ኢትዮጵያን የወከለችውና በውድድሩ ላይ ‹‹ሚስ ኢትዮጵያ›› ተብላ ስትጠራ የነበረችው ሀሴት ደረጄ 2ተኛ ሆናለች፡፡ ሀሴት ከአለም 2ተኛ ትሁን እንጂ ከአፍሪካ 1ኛ በመሆን ከአህጉሪቱ ቆነጃጅት ሁሉ ቀዳሚ በመሆን አሸናፊ መሆኗን የውድድሩ አዘጋጆች አስታውቀዋል፡፡

ከአለም 3ተኛ የወጣችው የፖላንድ ተወዳዳሪዋ ስትሆን የማርቲንኪ ተወዳዳሪዋ 4ተኛ ሆናለች፡፡ ይህ ውድድር ለአንድ ወር በህንድ የተለያዩ ግዛቶች ሲከናወን የቆየ ሲሆን ውድድሩን ዘሀበሻ ሲዘግብላችሁ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

MissWorld2025 #MissEthiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...