በህንድ እየተከናወነ ያለው ሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር አሁን ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ በዚህ ውድድር የ109 አገራት ቆነጃጅት የተሳተፉ ሲሆን ‹‹ሚስ ወርልድ›› የሚል መጠሪያ በማግኘት የዘንድሮውን ዘውድ የጫነችው ታይላንዳዊቷ ኦፓል ሱቻታ ሆናለች፡፡
እሷን ተከትላ ኢትዮጵያን የወከለችውና በውድድሩ ላይ ‹‹ሚስ ኢትዮጵያ›› ተብላ ስትጠራ የነበረችው ሀሴት ደረጄ 2ተኛ ሆናለች፡፡ ሀሴት ከአለም 2ተኛ ትሁን እንጂ ከአፍሪካ 1ኛ በመሆን ከአህጉሪቱ ቆነጃጅት ሁሉ ቀዳሚ በመሆን አሸናፊ መሆኗን የውድድሩ አዘጋጆች አስታውቀዋል፡፡
ከአለም 3ተኛ የወጣችው የፖላንድ ተወዳዳሪዋ ስትሆን የማርቲንኪ ተወዳዳሪዋ 4ተኛ ሆናለች፡፡ ይህ ውድድር ለአንድ ወር በህንድ የተለያዩ ግዛቶች ሲከናወን የቆየ ሲሆን ውድድሩን ዘሀበሻ ሲዘግብላችሁ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
