ሌ/ጄነራል ታደሰ አዲስ አበባ ገቡ !

Date:

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ቀጣይ እጣ ፈንታ ምን ይሆን?

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ፣ በክልሉ ወቅታዊና አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ዛሬ እሁድ መጋቢት 27 ቀን 2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ጄነራሉ በቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ከከፍተኛ የፌደራል ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው እንደሚመክሩ የተገለጸ ሲሆን፣ ጉብኝቱ በትግራይ ክልል ባለው የጸጥታና የፖለቲካ ሁኔታ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ምንጮች ጠቁመዋል።

ይህ ጉዞ ትልቅ ትኩረት የሳበው ጄነራል ታደሰ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ተሰጥቷቸው የነበረው የአንድ ዓመት የሥልጣን ጊዜ ከሦስት ቀናት በኋላ (መጋቢት 30) ስለሚያበቃ ነው።

ጄነራሉ ለተጨማሪ ስድስት ወራት በሥልጣን ላይ ይቆያሉ ወይስ አዲስ ምትክ ይመደባል የሚለው ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ አነጋጋሪ ሆኗል። የአዲስ አበባው ውይይትም የጊዜያዊ አስተዳደሩን ቀጣይ እጣ ፈንታና የክልሉን የሽግግር ሂደት የሚወስን ወሳኝ ክስተት እንደሚሆን ይጠበቃል።

አውራምባ ታይምስ –

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ውጭ ምንዛሪ የሚያድኑ የሴራሚክ ምርቶች በቅርቡ ለገበያ ይቀርባሉ

ይህ የተገለፀው ኢትዮደር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በ”Golden Tier...

የዓለም የቡና ገበያ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ተገለጠ

በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና አቅርቦት ላይ ተፈጥሮ የነበረው ስጋት...

አሜሪካ የኢራንን የጭነት መርከብን መያዟን አስታወቀች

በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን የዘጋችው...