ሕዝበ ሙስሊሙ የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ጥሪ ተላለፈ

Date:

ሕዝበ ሙስሊሙ ለመጅሊሱ ምርጫ ከነገ ጀምሮ ለ12 ቀናት የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ኮሚቴው ጥሪ አስተላለፈ።

ሕዝበ ሙስሊሙ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (ለመጅሊስ) ምርጫ ለማድረግ፣ ከነገ ጀምሮ በአቅራቢያው በሚገኝ የወረዳው መስጅድ የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ጥሪ ማድረጉን ኢፕድ ዘግቧል።

የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር አብዱልዋሲዕ ዩሱፍ ዓሊ እንዳሉት፤ ላለፉት 5 ወራት ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው ቦርዱ፣ በ2017 ዓ.ም ለሚካሄደው የመጅሊስ ምርጫ ዝግጅቱን አጠናቅቋል። በነገው ዕለትም ምዝገባ ይጀምራል ብለዋል።

ምርጫ ቦርዱ ምርጫውን አሳታፊና አካታች በሆነ መልኩ ለማካሄድ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ገልጿል፡፡

በመሆኑም ሕዝበ ሙስሊሙ መታወቂያውን በመያዝ፣ ከነገ ጀምሮ ለ12 ቀናት በየመስጅዱ በሚደረገው የመራጮች ምዝገባ ተመዝግቦ የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ቦርዱ ጥሪ አቅርቧል።

በምዝገባው ሂደት ለሚያጋጥሙ ቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት በየመስጅዱ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ መቋቋሙም በመግለጫው መጠቆሙን ኢፕድ በዘገባው አመልክቷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...