ሰአሊ ብሩክ የሺጥላ የብርሃን ለህጻናት ግብረ ሰናይ ድርጅት የክብር አምባሳደር ሆነ

Date:

ለበርካታ ህጻናት ህይወት መቀየር ምክንያት መሆኑን ያነሳው ሰአሊ ብሩክ የሺጥላ በተሰጠው ሀላፊነት ደስተኛ መሆኑንና የተጣለበትን አደራ ለመወጣት እንደሚሰራ ተናግሯል።

በዝግጅቱም ብሩክ ለብርሃን ህጻናት ግብረ ሰናይ ድርጅት በቀለማት ህብር ያሸበረቀ የስዕል ሥራውን በስጦታ አበርክቷል።

ድርጅቱ አካል ጉዳተኛ ህጻናትን እንዲሁም ልጃገረዶችና ቤተሰቦቻቸውን ተደራሽ የሚያደርጉ ድጋፎችን በማቅረብ የሚሰራ እንደሆነም ተገልጿል።
በተለይ በኦሮሚያ፣ አማራ፣ አፋር፣ ሲዳማ ክልሎች እና መካከለኛው ኢትዮጵያ ለ30 አመታት ሲሰራ ቆይቷል።

በXነዚህ ጊዜያት ከ23 ሺህ በላይ ህጻናትን ሲያግዝ እንደነበረም ተጠቁሟል።

በተጨማሪም የግጭት አፈታትና የሰላም ግንባታ፣ ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል፣ የስርዓተ ፆታ ማካተት እና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ማስወገድ ላይ ይሰራል።

ድርጅቱ ዩኒሴፍ፣ ላይት ፎር ዘ ወርልድ ከተሰኙ እና ሌሎች አጋር አካላት  የፋይናንስ ድጋፍ እንደሚደረግለት ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ክፍሌ አቦቸር እና ‹‹ይህ ነው ምኞቴ…››

ሠሎሞን ለማ ገመቹ ግዮን መጽሔት :- ሻለቃ ከፍሌ አቦቸር ስለ...

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...