ሱዳን በጦርነቱ ዳፋ አንዳንድ ቤተሰቦች ሣር እየበሉ ነው

Date:

የሱዳን ጦር ሠራዊት (SAF) ካርቱም ከተማ የሚገኘውን ቤተመንግሥት በመቆጣጠር በሁለት ዓመቱ የርስ በርስ ጦርነት ወሳኝ የተባለውን ድል መቀዳጀቱ ተነገረ ። የሱዳን መንግሥታዊ ቴሌቪዥን ጦሩ ቤተመንግሥቱን ያስለቀቀው ከፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ (RSF) መሆኑን ዛሬ ማለዳ ዘግቧል ። ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ቤተመንግሥቱን ጨምሮ የሱዳን በርካታ ሰፈሮችን ለበርካታ ጊዜያት ተቆጣጥሮ ነበር ።

በሁለቱ የሱዳን ኃይላት መካከል ጦርነቱ ከዛሬ ሁለት ዓመት ግድም ማለትም (ሚያዝያ 7 ቀን፣ 2015 ዓ.ም) ከተቀሰቀሰ በኋላ ቤተመንግሥቱ ወዲያውኑ በፈጥኖ ደራሹ ኃይል ቁጥጥር ወድቆ ነበር ። ይህ ድል ለሱዳን ጦር ሠራዊት ታላቅ እመርታ እንደሆነ ቢገለጥም፤ ፈጥኖ ደራሹ ኃይሉ የካርቱም ደቡባዊ ክፍልን እና በዋና ከተማዪቱና ተጎራባቿ ኦምዱርማን ከተማ መካከል ያሉ ቦታዎችን አሁንም እንደተቆጣጠረ መሆኑ ተዘግቧል ።

ሁለት ዓመት በተጠጋው የሱዳን የርስ በርስ ጦርነት ከ28,000 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዘግቧል ።  ከሦስት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል ። ጦርነቱ በፈጠረው ረሐብ የተነሳ አንዳንድ ቤተሰቦች በሕይወት ለመቆየት ሣር እየበሉ መሆናቸውን የፈረንሣይ ዜና አገልግሎት (AFP) ዘግቧል ። 

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...