ስምረት ፓርቲ በትግራይ ክልል እየታየ ያለው ፖለቲካዊ እና ሰብአዊ ቀውስ እንዳሳሰበው ገለጸ

Date:

ዲሞክራስያዊ ስምረት ትግራይ – ስምረት ፓርቲ በትግራይ ክልል የከፋ ፖለቲካዊ እና ሰብዓዊ ቀውስ መፈጠሩን ገልጾ፣ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ስምምነቱን በመጣስ የክልሉን ሰላም እና ደኅንነት አደጋ ላይ ጥሎታል ብሏል።

የአሁኑ የክልሉ አስተዳደር የሕዝብን ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ የቡድን ጥቅሙን ለማስጠበቅ ወደ ጦርነት መግባቱን በትላንትናው እለት ባስራጨው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተሰጠ መግለጫው ጠቁሟል።

አስተዳደሩ በውጭ ኃይሎች ተልዕኮ በመመራት ትግራይን ለከፋ ችግር ዳርጓል ያለው ፓርቲው፤ በክልሉ እየታየ ያለው ሰብአዊ ቀውስ እንዳሳሰበው ገልጿል።

በክልሉ እየተካሄደ ያለው ሕገ-ወጥ የንብረት ሽያጭ እና ዘረፋ ሌላው የድርጅቱ ስጋት ነው።

በተለይም በሕግ የተጠበቁ ቅርሶች እና ሕንፃዎች ለይስሙላ ጨረታ ቀርበው መሸጣቸው ተቀባይነት እንደሌለው ገልጾ፣ ባለሀብቶች ከዚህ ተግባር እንዲቆጠቡ መክሯል።

ወጣቶች ከፍላጎታቸው ውጭ ወደ ጦር ግንባር እየተወሰዱ መሆኑን የጠቀሰው ፓርቲው፣ ይህ ድርጊት የትግራይን አንድነት የሚፈታተን መሆኑን አስታውቋል።

በደቡብ ትግራይ በደረሰ የድሮን ጥቃት እና ግጭቶች ለደረሰው ጉዳት የጦርነት ቀስቃሽ አካላት ተጠያቂ መሆናቸውንም ገልጿል።

ዲሞክራስያዊ ስምረት ትግራይ ፓርቲ በክልሉ የተፈጠረውን ቀውስ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ከሌሎች ለውጥ ፈላጊ ኃይሎች ጋር እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።

ፌዴራል መንግሥት እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በክልሉ ሰላም እንዲሰፍን ድጋፍ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...