ሾዴ የተባለው የሸኔው መሮ ዋና ሰው ተገደለ ተባለ

Date:

ሾዴ እየተባለ የሚጠራው የሸኔው መሮ ዋና ሰው እንደሆነ የሚታወቀው መገደሉ ተገለፀ።

የመሮ ዋናው ሰው የነበረው እንዲሁም በታንዛኒያው ድርድር ከጫካ ወጥቶ ታንዛኒያ ዳሬሰላም ድረስ ከመሮ ጋር ተጉዞ የሸኔ ሽብር ቡድን ተደራዳሪ የነበረው ሾዴ በተወሰደበት እርምጃ ተገድሏል።

ሾዴ የተባለው የሽብር ቡድኑ አመራር ከታንዛኒያ መልስ የአጠቃላይ የወለጋ ዞኖች አዛዥ ተደርጎ በመሮ ተሹሞ የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ነው።

ሾዴ የተገደለው ምስራቅ ወለጋ ዞን ሃሮ ሊሙ ወረዳ ገንጂ አካባቢ ከኮርማ ወንዝ ወደ ሱጊ በሚወሰደው መንገድ ላይ በሞተር ሳይክል ተደብቆ ሲጓዝ የፀጥታ ኃይሎች ባገኙት መረጃ መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም አመሻሽ ላይ እርምጃ ተወስዶበታል።

ከሾዴ ጋር አብረው አጅበው ሲጓዙ የነበሩ በርካታ የሸኔ ሽብር ቡድን አባላትም ተደምስሰዋል።

ከሠሞኑ በሰሜን ሸዋ ዞን እና በሌሎችም አካባቢዎች የአሸባሪው ሸኔ ታጣቂዎች ክፉኛ እየተመቱ በቁጥጥር የዋሉ ሲሆን አሁንም ቢሆን የሸኔ ታጣቂዎች የመከላከያ ሠራዊቱን ምት መቋቋም ተስኗቸው እየተፍረከረኩ እጅ እየሠጡ እየተማረኩ እርምጃ እየተወሰደባቸውና እየተበተኑ ይገኛሉ።

ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...