የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በለጋሾች አስተዋፅዖ መቀነስ ሳቢያ የ2026ን በጀት በ17 በመቶ በመቀነሱ በዓለም ዙሪያ የሰው ኃይል ቅነሳ አድርጓል።
ኮሚቴዉ በለጋሾች አስተዋፅዖ መቀነስ ምክንያት የ2026 በጀቱን በ17 በመቶ በመቀነስ ወደ 2,900 የሚጠጉ የሙሉ ጊዜ የሥራ ቦታዎችን በዓለም ዙሪያ እንደሚያስወግድ አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት ከ18 ሺህ በላይ ሠራተኞች ያሉት ኮሚቴው በከፍተኛ የሰብዓዊ እርዳታ ፍላጎት ወቅት ይህን ከባድ ውሳኔ ለመውሰድ ተገድዷል።
ICRC ለ 2026 ዓመት የ1.8 ቢሊዮን የስዊስ ፍራንክ ($2.2 ቢሊዮን) በጀት አጽድቋል—ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ17 በመቶ ቅናሽ ያሳያል።
ይህ ቅናሽ ድርጅቱ ከ18 ሺህ በላይ ከሆኑ ሰራተኞቹ ውስጥ ወደ 2,900 የሚጠጉ የሙሉ ጊዜ የሥራ ቦታዎችን እንዲቀንስ ያስገድደዋል።
የኮሚቴው ፕሬዝዳንት ሚሪያና ስፖልያሪች፥ “የጦርነት መባባስ፣ የእርዳታ ፈንድ ላይ የሚደረጉ ቅናሾች እና የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ሕግ ጥሰቶች ሥር የሰደደ መቻቻል አደገኛ በሆነ ሁኔታ እየተገጣጠሙ ነው” በማለት የችግሩን አስከፊነት ገልጸዋል።
