በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

Date:

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል የሚተላለፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም እንደማይጠበቅባቸው የአሜሪካው ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ገለጹ።

ምክትል ፕሬዝዳንቱ ከሲኤንቢሲ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃል ምልልስ “የሆርሙዝ ወሽመጥ ለረዥም ጊዜ ከክፍያ ነጻ ይሆናል ብለን እንጠብቃለን” ብለዋል።

ጦርነቱ መነሳቱን ተከትሎ ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ ለሚያልፉ መርከቦች የክፍያ ሥርዓት ዘርግታ ቆይታለች።

አሁን ከአሜሪካ ጋር በተደረሰው ስምምነት አማካኝነት በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ያለ ክፍያ ማለፍ ጊዜያዊ ሊሆን እንደሚችል የተናገሩት ጄዲ ቫንስ፤ ዘላቂ መፍትሔ ለማግኘት ከኢራን ጋር መወያየት እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።

ክፍያውን ማስቀረት “በቴክኒክ ድርድሩ ወቅት የምናነሳው ጉዳይ ይሆናል። አብረን በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠን የምንወያይባቸው በጣም ጠቃሚ ነጥቦች ይኖራሉ” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በሀገራችን የባህል ሙዚቃ ዘርፍ ታዋቂነትን ያተረፈውና በብዙሃን ዘንድ ሰሜ...