በሶሪያ የሚንቀሳቀሱ ወታደራዊ ኃይሎች በሀገሪቱ የመከላከያ ሠራዊት ሥር ተዋሃዱ

Date:

በሶሪያ የሚንቀሳቀሱ ሁሉም ወታደራዊ ኃይሎች በመከላከያ ሠራዊት ሥር መዋሃዳቸውን የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር ሙርሃፍ አቡ ቃስራ ገለጹ።

ሂደቱ ሁሉንም የሀገሪቱን ወታደራዊ ኃይሎች በአንድ ተቋማዊ ማዕቀፍ ሥር ለማዋቀር የተደረገው ሥራ ውጤት መሆኑ ነው የተገለጸው።

አቡ ቃስራ በኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “ከተቋማዊ ሥራ አስፈላጊነት አንፃር፣ የተቀሩት ወታደራዊ ቡድኖችም ይህ መግለጫ በወጣ በ10 ቀናት ውስጥ አንዲቀላቀሉን እናሳስባለን” ብለዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም በዚህ ትዕዛዝ ላይ የሚዘገይ ወይም ውሳነውን የማይቀበል ማንኛውም ዓይነት ወታደራዊ ቡድን ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድበት አሳስበዋል።

ትዕዛዙ የመጣው በጥር ወር መገባደጃ ላይ አሳድን ከሥልጣን ያስወገዱት ኃይሎች ቁልፍ መሪ አህመድ አል ሻራ መሪነት በተደረገው ስብሰባ የሶሪያ ወታደራዊ ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር ሥር ለማድረግ ከተስማሙ በኋላ መሆኑን አናዶሉ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአሜሪካ ጦር እስራኤልን ከኢራን መከላከሌን ላቆም እችላለሁ አለ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ...

በፌደራሉ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መቀስቀሱ ተገለጸ

ከሱዳን ጋር በሚዋሰነው የሰሜናዊ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል ውስጥ በሚገኝ...

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...