በሶሪያ የሚንቀሳቀሱ ወታደራዊ ኃይሎች በሀገሪቱ የመከላከያ ሠራዊት ሥር ተዋሃዱ

Date:

በሶሪያ የሚንቀሳቀሱ ሁሉም ወታደራዊ ኃይሎች በመከላከያ ሠራዊት ሥር መዋሃዳቸውን የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር ሙርሃፍ አቡ ቃስራ ገለጹ።

ሂደቱ ሁሉንም የሀገሪቱን ወታደራዊ ኃይሎች በአንድ ተቋማዊ ማዕቀፍ ሥር ለማዋቀር የተደረገው ሥራ ውጤት መሆኑ ነው የተገለጸው።

አቡ ቃስራ በኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “ከተቋማዊ ሥራ አስፈላጊነት አንፃር፣ የተቀሩት ወታደራዊ ቡድኖችም ይህ መግለጫ በወጣ በ10 ቀናት ውስጥ አንዲቀላቀሉን እናሳስባለን” ብለዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም በዚህ ትዕዛዝ ላይ የሚዘገይ ወይም ውሳነውን የማይቀበል ማንኛውም ዓይነት ወታደራዊ ቡድን ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድበት አሳስበዋል።

ትዕዛዙ የመጣው በጥር ወር መገባደጃ ላይ አሳድን ከሥልጣን ያስወገዱት ኃይሎች ቁልፍ መሪ አህመድ አል ሻራ መሪነት በተደረገው ስብሰባ የሶሪያ ወታደራዊ ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር ሥር ለማድረግ ከተስማሙ በኋላ መሆኑን አናዶሉ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...