በባንግላዲሽ የአየር ኃይል ጄት አደጋ የበርካታ ሰዎች ህይወት አለፈ

Date:

በባንግላዲሽ ዋና ከተማ ዳካ የአየር ኃይል ማሰልጠኛ ጄት አውሮፕላን ተከስክሶ ቢያንስ 19 ሰዎች ሲሞቱ 164 ሰዎች ቆስለዋል።

አደጋው የደረሰው የF-7 BGI የተሰኘ የአየር ሀይል ጄት ለልምምድ በተነሳ በጥቂት ደቂቃ ውስጥ በዳካ በሚገኝ ትምህርት  ቤት ጊቢ  የተከሰከሰ ሲሆን ቢያንስ 19 ሰዎች ለሞት ተዳርገዋል ።

ከሟቾቹ መካከልም የአውሮፕላኑ አብራሪ እና በርካታ ተማሪዎች ይገኙበታል  የተባለው ሲሆን በአደጋው ሰለባ የሆኑ ተማሪዎች

እድሜያቸው ከአራት እስከ 18 ዓመት መካከል እንደሆነ ተገልጿል ።

የአየር ኃይል ጀቱ ሚልስተን ኮሌጅ እና  ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ሲለሰከስ ተማሪዎች ትምህርት ቤት ውስጥ እንደነበሩ ተዘግቧል።

ከባንግላዲሽ አየር ኃይል ኩርሚቶላ ቤዝ ከተነሳ ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ባጋጠመው  የቴክኒክ ችግር ምክንያት አውሮፕላኑ ሊከሰከስ እንደቻለ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ሌተና ኮሎኔል ሳሚ ኡድ ዶውላ ቾውዱሪ ተናግረዋል። ዘገባው የሮይተርስ ነው

NBC Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...