በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት “ሊፈነዳ ተቃርቧል”

Date:

ኤርትራ፣ ሠራዊቷን ክተት እንዳላወጀችና በኢትዮጵያ ላይ “የወታደራዊ ትንኮሳ ድርጊቶችን” እንዳልፈጸመች በመግለጽ አሜሪካ በሚገኘው ኤምባሲዋ በኩል ባወጣችው መግለጫ አስተባብላለች።

ይልቁንም በቀጠናው ውጥረት ያሰፈነው፣ ኢትዮጵያ “በዲፕሎማሲ” ወይም “በወታደራዊ ኃይል” ወደብ ማግኘት አለብኝ በማለት የከፈተችው ዘመቻ ነው በማለት ኤርትራ መክሰሷን ዋዜማ ዘግባለች፡፡

ኤርትራ ይህን ያለችው፣ የአሜሪካ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰሞኑን በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ላካሄደው የስሚ መድረክ በሰጠችው ምላሽ ነው።

ቋሚ ኮሚቴው በኤርትራ ላይ “ያልተረጋገጡ” ውንጀላዎችን አቅርቧል በማለት የከሰሰው የኤርትራ መግለጫ፣ ለቋሚ ኮሚቴው አስረጅ ኾነው የቀረቡ ባለሙያዎች ለውጥረቱ ምንጩ ‘የኤርትራ ወታደሮች የትግራይ ግዛቶችን ተቆጣጥረው መቀጠላቸው’ ነው ማለታቸውን አጣጥሏል።

ሴናተር ክሪስ ቫን ሆለን በመድረኩ ላይ፣ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት “ሊፈነዳ ተቃርቧል” በማለት መናገራቸውን ኤርትራ ጠቅሳለች።

ዋዜማ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...