በዳሰነች ወረዳ 34 ቀበሌዎች ‘ሙሉ በሙሉ’ በኦሞ ወንዝ ሙላት ተጥለቀለቁ

Date:

በ #ደቡብ_ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በዳሰነች ወረዳ 34 ቀበሌዎች ‘ሙሉ በሙሉ’ በኦሞ ወንዝ ሙላት መጥለቅለቃቸውና 81 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸውን ነዋሪዎች እና የመንግስት ኃላፊ ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

“የኦሞራቴ ከተማ በውሃ ተከባለች፤ የጎርፍ መጥለቅለቁ ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ከተማችን ሊገባ ይችላል፤ እጣፈንታችንን ቁጭ ብለን እየተጠባበቅን ነው” ሲሉ ስማቸውን እንዳይጠቀስ የጠየቁ በኦምራቴ ከተማ ነዋሪ ተናግረዋል።

ሌላኛው ስሜ ባይጠቀስ ያሉ እና በጎርፍ መጥለቅለቁ ምክንያት ተፈናቅለው ነበረሙስ በተባለ መጠለያ ተጠልለው የሚገኙ ነዋሪ በበኩላቸው፤ “የእርሻ ቦታዎችን ሁሉ ጠራርጓል። ቤቶችን አፍርሷል። ኦሞራቴ ከተማን ለመዋጥ ደግሞ አንድ ኪ.ሜ እንኳን አይሞላም የተቃረበው” ብለዋል።

ስማቸውም ሆነ የስራ ሀላፊነታቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የኦሞራቴ ከተማ የመንግስት ሀላፊ፤ የኦሞ ወንዝ ሞልቶ የቱርካና ሀይቅ ከኦሞራቴ ከተማ ከዚህ ቀደም ከነበረው 60 ኪ.ሜ ርቀት አሁን ላይ ወደ 1.3 ኪ.ሜ ርቀት ላይ መጠጋቱን ጠቅሰዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...