በፀሐይ ኃይል የሚሰራው ግዙፉ የመኪና ማጓጓዣ መርከብ የመጀመሪያ ጉዞውን አጠናቀቀ

Date:

የዓለማችን ትልቁ በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የመኪና ማጓጓዣ መርከብ “ዩዋን ሃይ ኮው” (Yuan Hai Kou) የመጀመሪያ ጉዞውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቆ በግሪክ ፒሬየስ ወደብ መድረሱን የቻይና ኮስኮ ሺፒንግ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ (China COSCO Shipping Corporation Limited) አስታወቀ። መርከቡ 4,000 የቻይና ተሽከርካሪዎችን ጭኖ በሰላም ደርሷል ነው የተባለው፡፡

ይህ ዘመናዊ መርከብ በፀሐይ ኃይል የሚሰራ በመሆኑ ለአካባቢ ጥበቃ ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። የ”ዩዋን ሃይ ኮው” መምጣት በባህር ትራንስፖርት ኢንዱስትሪ ውስጥ የዘላቂነት እና የቴክኖሎጂ እድገት ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል ነው የተባለው።

የቻይና ኮስኮ ሺፒንግ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ ይህ መርከብ የካርበን ልቀትን በመቀነስ እና የአካባቢን ተፅእኖ በመቀነስ ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ገልጿል።

የመርከቡ የመጀመሪያ ጉዞ ስኬታማ መሆን የቻይናን በባህር ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን የቴክኖሎጂ አቅም የሚያሳይ ሲሆን፣ ለወደፊት ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ የትራንስፖርት አማራጮችን ለማስፋፋትም መንገድ ይከፍታል ተብሎለታል።

menahriafm

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...