ብዕርና ባሩድ በአሜሪካ በካናዳና በአውሮፓ ገበያ ላይ ዋለ

Date:

በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ አያሌ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በደማቅ ሥነ ሥርዓት የተመረቀው የአንዱዓለም አራጌ አዲስ መጽሐፍ ብዕርና ባሩድ በአሜሪካ ታትሞ በተለያዩ ከተሞች ለገበያ ቀርቧል።

ብዕርና ባሩድ በአሁኑ ወቅት በዋሽንግተን ዲሲ፣ በሲልቨር ስፕሪንግ፣ በቨርጂኒያ፣ በሂውስተን፣ በዴንቨር፣ በዳላስ፣ በኦክላንድና ሳንሆዜ በሽያጭ ላይ ይገኛል።

በተጨማሪም በካናዳ ቶሮንቶ ለአንባቢዎች ደርሷል።

በአውሮፓ ደግሞ በጀርመን ፍራንክፈርትና በርሊን፣ በስዊዘርላንድ፣ በሆላንድ አምስተርዳም እንዲሁም በስዊድን ስቶክሆልም ለአንባቢዎች መቅረቡ ታውቋል።

ይህ አዲስ መጽሐፍ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሰንሰለት በጥልቀት የሚፈትሽና ብዙ የሚያወያዩ ቁምነገሮችን የያዘ ሲሆን፣ ለሀገራዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄዎችን የሚያመለክት ድንቅ ሥራ መሆኑ ተገልጿል።

መጽሐፉን በኢትዮጵያ ገበያ ለማቅረብ ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚገኙ የአንላይን ተጠቃሚዎችም በቅርቡ በአማዞን ላይ እንደሚጫን ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...