በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዘለቀ ተመስገን እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ አማካሪ አምባሳደር ግርማ ብሩ ጋር በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል የመንግሥትና የግሉ ዘርፍ የጋራ ውይይት መርተዋል።
ውይይቱ የንግድ ዲፕሎማሲን ማጠናከር፣ የገበያ ተደራሽነትን ማስፋት እና በኢትዮጵያ ለሚሰሩ የአሜሪካ ኩባንያዎች ፍትሃዊ የንግድ ሁኔታ መፍጠር ላይ ያተኮረ ነበር።
አምባሳደር ማሲንጋ ግልጽ፣ ተጠያቂነት ያለውና ሊገመት የሚችል የንግድ አካባቢ መፍጠር የአሜሪካን ኢንቨስትመንት ለመሳብና በግሉ ዘርፍ የሚመራ የኢኮኖሚ እድገት ለማፋጠን ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩ ላይ የአሜሪካ ንግድ ተቋማት ተወካዮች ያቀረቧቸው ችግሮችና መፍትሔ ሀሳቦች በመንግሥት ኃላፊዎች በቀጥታ ምላሽ ያገኙ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የግሉ ዘርፍ ተወካዮች ያሉባቸውን ማነቆዎች ለመፍታት የተግባር ዕቅድ እንዲያዘጋጁ ሐሳብ ቀርቧል።
አሜሪካ ይህ ትብብር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ለማፋጠን፣ የንግድ እንቅስቃሴን ለማስፋትና ለሁለቱም አገራት ሕዝቦች የኢኮኖሚ ጥቅም ለማሳደግ እንደሚያግዝ ገልጻለች።
