አዲስ አበባ የአፍሪካ የሎጂስቲክስ ማኅበር ዋና መቀመጫ ሆና ተመረጠች

Date:

በቱርክ ኢስታንቡል እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ የሎጂስቲክስ ማኅበራት ጉባኤ፥ አዲስ አበባ ከተማን የማኅበሩ ዋና መቀመጫ አድርጎ መምረጡ ተገለጸ።

ይህን የገለጹት ኢትዮጵያን ወክለው በጉባኤው ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የኢትዮጵያ የዕቃ አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማኅበር አቶ ዳዊት ውብሸት ናቸው።

በቱርክ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባኤ ላይ 35 ሀገራት ተሳታፊ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ዳዊት ውብሸት፥ ኢትዮጵያ የቦርድ ወንበር ማግኘቷንም ይፋ አድርገዋል።

የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ይህን ያስታወቁት የሎጂስቲክስ እና ትራንስፖርት ዘርፍ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና የዩኒቨርሲቲዎች የጋራ የምክክር መድረክ እየተከናወነ በሚገኝበት መድረክ ላይ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት ነው።

ኢትዮጵያ በ2027 የሚካሄደውን የዓለም የእቃ አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማህበር (ፊያታ) ጠቅላላ ጉባኤን በመዲናዋ አዲስ አበባ እንደምታስተናግድም ተገልጿል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...