ኢትዮጵያ በስታርትአፕ በዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንድትሆን ነዉ

Date:


የስታርትአፕ አዋጅ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንድትሆንና ያላትን ዕምቅ አቅም በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማስመዝገብ እንደሚያሰችል የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባው፤ የኢትዮጵያ የስታርትአፕ አዋጅ አፅድቋል።

የሰው ሀብት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ እንደተናገሩት፤ አዋጁ ምቹ የስታርታአፕ ምህዳርን በመገንባትና የተቀናጀ ድጋፍ መስጠት በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።

ረቂቅ አዋጁ የፈጠራ ባለሙያዎችን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያበረታታ ተገልጿል። ትውልድ ራሱ ፈጥሮ፣ ራሱ አምርቶ ራሱ አቅራቢ እንዲሆን የሚያስችል ስለመሆኑ ተገልጿል።

አዋጁ በዓለም አቀፍ ደረጃ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ የተደገፉ ትላልቅ ኢንዱስትሪዎችንና ኩባንያዎችን በማፍራት ለኢኮኖሚ ዕድገትና ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑንም ገልፀዋል።

የፋይናንስ አቅርቦት ተግዳሮትና ስጋትን በዘላቂነት ለመቅረፍ የግራንት ፕሮግራም፣ የብድር ዋስትና ማዕቀፍና መዋቅር ማደራጀት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

በክብረአብ በላቸው

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ቀይሮታል!” — ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

በ"ወቸው ጉድ" ፖድካስት ላይ እንግዳ ሆነው የቀረቡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ...

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...