ኢትዮጵያ ከቡና የውጪ ንግድ በሀገሪቱ ታሪክ ከፍተኛውን ገቢ ሰበሰበች

Date:

በበጀት ዓመቱ 10 ወራት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ የቡና ኤክስፖርት አፈጻጸም መመዝገቡን የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

ሀገሪቱ በ10 ወራት ውስጥ ከቡና ብቻ ከ1 ነጥብ 8 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ላይ ገቢ ማግኘቷንም የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ ባለስልጣኑ በበጀት ዓመቱ 10 ወራት 354 ሺህ 302 ቶን ቡና ወደ ውጭ መላኩን ጠቁመዋል፡፡

ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በመጠን የ145 ሺህ 316 ሺህ ቶን፣ በገቢ ደግሞ የ869 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ እንዳለው አስታውቀዋል፡፡

በ10 ወራት የኢትየጵያ ቡና ቀዳሚ መዳረሻ ሀገራትም በቅደም ተከተል ጀርመን፣ ሳዑዲ አረቢያ እናአሜሪካ እንደነበሩም አስታውሰዋል፡፡

ለተመዘገበው ስኬት ከመንግስት ጋር በቅንጅት ርብርብ ላደረጉ አካላትም ዋና ዳይሬክተሩ ምስጋና ማቅረባቸውን ከባለስልጣኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...