ኢትዮጵያና የአውሮፓ ኅብረት ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

Date:

ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችላቸውን ስትራቴጂካዊ የአጋርነት ትብብር ስምምነት መፈራረማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ገለጸ።

“ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ” በሚል ስያሜ የተፈረመውን የትብብር ስምምነት ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ያስቆጠረውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በማሳደግ በአውሮፓውኣን 2016 ለተፈረመው የስትራቴጂያዊ ትብብር ስምምነት ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑም ተመላክቷል።

ስምምነቱን በኢትዮጵያ በኩል ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ እና በአውሮፓ ኅብረት በኩል የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ፈርመዋል።

የትብብር ስምምነቱ በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በምግብ ሥርዓት፣ በጤና በመሰረተ ልማት እንዲሁም በሰላምና ጸጥታ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የአውሮፓ ኅብረት “ግሎባል ጌትዌይ” በኢትዮጵያ እና በኅብረቱ መካከል የጋራ ስትራቴጂያዊ ራዕይ ለመቅረፅና አጋርነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር በትክክለኛው ወቅት ይፋ መደረጉን ፕሬዚዳንት ታዬ ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ኅብረት መካከል ላለው የረጅም ጊዜ አጋርነት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑንም ፕሬዚዳንት ታዬ እና የአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን በጋራ በሰጡት መግለጫ አረጋግጠዋል።

(#አዲስ_ማለዳ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...