ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በኢዩጂን ዳይመንድ ሊግ ውድድር

Date:

ትናንት በኢዩጂን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉበት የወንዶች 10 ሺህ ሜትር ፣የሴቶች 5 ሺህ ፣800 ሜትር እና 1500 ሜትር ውድድር ተካሂዷል ።

በወንዶች 10ሺህ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ 1-3 በመውጣት ድል ተቀዳጅቷል ።

አትሌት ቢኒያም መሀሪ ውድድሩን በ 26:43.82 በመግባት ሲያሸንፍ ፣አትሌት በሪሁ አረጋዊ 26:43.84 በመግባት ሁለተኛ ሲወጣ
አትሌት ሰለሞን ባረጋ 26: 44.13 በሆነ ሰዓት ሶስተኛ ደረጃ ይዘዋል ።

በ5ሺህ ሴቶች ውድድር የፓሪስ ኦሎምፒክ የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር ሻምፒዮናዋ ቢያትሪስ ችቤት የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር አሸንፋለች ።

አትሌት ቢያትሪስ ችቤት 13:58.06 በመግባት በአትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን አሻሽላለች ።

በውድድሩ ላይ ኬንያዊቷ አትሌት ንጌቲች ሁለተኛ ስትወጣ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በ14:04.41 ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

በ800 ሜትር ሴቶች ውድድር አትሌት ፅጌ ዱግማ 1:57.10 በመግባት በአንደኝነት አሸንፋለች ።

በ1500 ሜትር ውድድር ኬንያዊቷ አትሌት ፌዝ ኪፒዮጎን በ3:48.68 በመግባት በራሷ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸንፋለች።

በውድድሩ ላይ የተሳተፈችው አትሌት ድርቤ ወልተጂ በ3:51.44 በመግባት ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቃለች ።

በሌላ ዜና በፈረንሳይ ናንሲ በተካሄደው የ800 ሜትር የሴቶች ውድድር አትሌትንግስት ጌታቸው 1:58.15 በመግባት ስታሸንፍ፣ በወንዶች ውድድር አትሌት ዮሐንስ ተፈራ 1:44.49 በመግባት ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...