ኢንተር ሚላን በርካታ ደጋፊዎቹ የቅዳሜውን የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ ለመመልከት ጥያቄ ማቅረባቸው ተገልጿል።
ጨዋታውን ለመታደም ከ 80,000 በላይ የኢንተር ሚላን ደጋፊዎች የትኬት ጥያቄ ማቅረባቸው ተነግሯል።
የቀረበው የስታዲየም መግቢያ ትኬት ከሁለት አመታት በፊት በኢስታንቡል ፍፃሜ ከቀረበው የበለጠ እንደሆነ ተገልጿል።
የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር ለክለቦች ለእያንዳንዳቸው 18,000 ትኬቶች የሚሰጥ ሲሆን ኢንተር ሚላን ለታማኝ ደጋፊዎቹ ቅድሚያ እንደሚሰጥ አሳውቋል።
የሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ የፊታችን ቅዳሜ በጀርመን ሙኒክ አሊያንዝ አሬና ስታዲየም ይካሄዳል።
@Tikvahethsport
