እስራኤል በኢራን የኒውክሌር ኃይል ላይ ጥቃት ለመፈፀም መዘጋጀቷን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ ከ1 በመቶ በላይ ጨምሯል።
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ የሀምሌ ወር ዋጋ 68 ሳንቲም ወይም 1.04 በመቶ ከፍ ብሏል።
በዩናይትድ ስቴትስ የዌስት ቴክሳስ መካከለኛ የሀምሌ ወር የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ የወደፊት እጣ 70 ሳንቲም ወይም 1.1 በመቶኛ ጨምሮ ወደ 62.73 ዶላር ከፍ ብሏል።
በዩናይትድ ስቴትስ የተገኘ አዲስ መረጃ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር መስሪያ ቤቶችን ለመምታት በዝግጅት ላይ መሆኗን ሲኤንኤን ጉዳዩን ከሚያውቁ በርካታ የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል።
ባለሥልጣኖቹን ጠቅሶ ሲ ኤን ኤን አክሎ እንደዘገበው የእስራኤል መሪዎች ጥቃት ለመፈፀም የመጨረሻ ውሳኔ ማድረጋቸው ግልጽ አይደለም ብለዋል።
“እንዲህ ዓይነቱ የውጥረት መባባስ የኢራንን የነዳጅ አቅርቦትን አደጋ ላይ የሚጥል ብቻ ሳይሆን በሰፊው ሰፊው ክልል ውስጥም ጭምር አደጋ የሚደቅን ነው” ሲሉ የሸቀጦች ስትራቴጂስቶች ገልፀዋል።
ኢራን በፔትሮሊየም ላኪ አገሮች ድርጅት ውስጥ በሦስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን የእስራኤል ጥቃት ከአገሪቷ የሚመጡትን የነዳጅ ፍሰት ሊረብሽ ይችላል።
በተጨማሪም ኢራን በባህረ ሰላጤው በሆርሙዝ ማለፊያ በኩል የሚተላለፈውን የነዳጅ ጫኝ በመዝጋት አፀፋውን ልትመልስ ትችላለች የሚል ስጋት አለ በዚህም ሳዑዲ አረቢያ ኩዌት ኢራቅ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ድፍድፍ ዘይት እና ነዳጅ ወደ ውጭ መላክ እንዳይችሉ ያደርጋል።
