“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

Date:

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋዊ የማኅበራዊ ገጻቸው ባስተላለፉት ጠንከር ያለ መልዕክት፥ እሳቸው በሥልጣን ላይ እስካሉ ድረስ ኢራን የኑክሌር ጦር መሣሪያ እንድትታጠቅ በፍጹም እንደማይፈቅዱ በድጋሚ አስታውቀዋል።

ይህ የኔታንያሁ መግለጫ የወጣው አሜሪካ እና ኢራን በክልሉ ያለውን ውጥረት ለማርገብ “የእስላማባድ ስምምነት” (Islamabad Agreement) የተሰኘ አዲስ የሰላም ስምምነት ለማድረስ እየተደራደሩ ነው በሚል ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ሰፊ ዘገባዎችን እያስተናገዱ ባሉበት ወቅት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው ላይ ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በዚህ ጉዳይ ላይ ሙሉ ስምምነት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፥ ላለፉት 30 ዓመታት የኢራንን የኑክሌር መርሃ-ግብር ለማደናቀፍ በግንባር ቀደምትነት ሲታገሉ መቆየታቸውንም አስታውሰዋል።

ኔታንያሁ አክለውም “ይህ ዘመቻ ባይኖር ኖሮ ኢራን እስራኤልን የሚያጠፉ የአቶሚክ ቦምቦችን ከታጠቀች ቆይታ ነበር” በማለት የጉዳዩን አሳሳቢነት ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...