እንግሊዛዊው ግሪን ሞሽን በኢትዮጵያ ውስጥ ሥራውን በይፋ ጀመረ

Date:

ኩባንያው በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ስራውን የጀመረ ሲሆን ወደ ሌሎች የሀገሪቱ ከተሞችም ለማስፋፋት እቅድ እንዳለው አስታውቋል።

ኩባንያው በኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ ለመጀመር የሁለት ዓመት ድርድር ማድረጉንና በሂደቱ ውስጥም የተለያዩ ተግዳሮቶች እንደገጠሙት ገልጿል።

በተለይም ዓለም አቀፍ የንግድ ልምዶችን እና የኢትዮጵያን የሕግ ማዕቀፍ ማጣጣም ትልቅ ፈተና እንደነበረበት አስታውቋል።

ግሪን ሞሽን ከኤክስፔዲያ እና ቡኪንግ.ኮም ከመሳሰሉ ዓለም አቀፍ የቦታ ማስያዣ መድረኮች ጋር የተዋሃደ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለአገር ውስጥና ለአለም አቀፍ ተጓዦች ምቹ አገልግሎት ለመስጠት በኢትዮጵያ ከሚገኘዉ ኤክሰለንስ መኪና ኪራይ ኩባንያ ጋር በሽርክና መስራቱን ገልጿል።

ኩባንያው በኢትዮጵያ ስራ በመጀመሩ የውጭ ምንዛሪ እንደሚያስገኝና ለአካባቢው ኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

Source: capitalethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...