ከ10 ህጻናት ስድስቱ ለነርቭ ዘንግ ችግር ይጋለጣሉ

Date:

በኢትዮጵያ የነርቭ ዘንግ ችግር የሌለባቸውን ልጆች መውለድ የሚችሉት 29 በመቶ ሴቶች ብቻ መሆናቸው ተገልጿል።

ከ10 እናቶች መካከል 6ቱ የነርቭ ችግር ያለባቸውን ህፃናት ሊወልዱ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት አጥኚ ዶክተር ማስረሻ ተሰማ ገልፀዋል።

የበሽታው ምክንያትም ምግብን በጠቃሚ ንጥረ ነገሮች አለማበልፀግ መሆኑ ተመላክቷል። ይህ የጤና ችግር ዜጎች የተስተካከለ የሰውነት ክፍል እንዳይኖራቸው ሊያደርግ እንደሚችል ተገልጿል።

የነርቭዘንግ ችግር ከተሰኘው የበሽታ አይነት ጋር በተያያዘ በዓመት ከ30 ሺሕ በላይ ህፃናት እንደሚወለዱ የሆፕ ኤስ ቢ ኤች ስራ አስኪያጅ ቤዛ በሻህ ገልፀዋል።

በበርካታ ሆስፒታሎች ህክምናው አለመኖሩ እና ዜጎች ቅድመ መከላከል ላይ ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ መሆን የበርካታ ህፃናት ህይወት እንደሚጠፋ ምክንያት መሆኑን ስራ አስኪያጇ ተናግረዋል።

የበሽታው ተጠቂ የሆኑ ግለሰቦች ሽንት መቆጣጠር የማይችሉ እና በራሳቸው መንቀሳቀስ የሚያዳግታቸው እንደሆኑም ተገልጿል።

(ሀገሬ ቴቪ)፤

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...