ኬንያ 200 የሚሆኑ ዜጎቿ ለሩሲያ እየተዋጉ እንደሆነ አስታወቀች

Date:

ዩክሬን ባለፈው ሳምንት 1400 የሚሆኑ አፍሪካውያን በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት እየተዋጉ መሆኑን ገልፃ እንደነበር ሲታወስ ኬንያ ከ200 የሚበልጡ ዜጎቿ ለሩሲያ እየተዋጉ ስለመሆኑና በርካታ ኤጀንሲዎች አሁንም ምልመላ እያደረጉ መሆኑን አስታውቃለች።

የኬንያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የምልመላ መረቦቹ በኬንያና በሩሲያ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሶ በሞስኮ የሚገኘው የኬንያ ኤምባሲ በጦርነቱ የተጎዱ ሰዎችን መመዝገቡንና ሰዎቹ እስከ 18,000 ዶላር ድረስ ሊከፈላቸው ቃል እንደተገበላቸው ገልጿል።

ባለፈው መስከረም ኬንያ በናይሮቢ አቅራቢያ ለጦርነቱ ምልመላ ሲያደርግ የነበረን ግለሰብ መያዟና ሊላኩ የነበሩ 21 ዜጎቿን ማትረፏ ይታወሳል።

በተጨማሪ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶም በዩክሬን የተያዙ ኬንያውያን እንዲለቀቁ የዩክሬን አቻቸውን መጠየቃቸው ይታወሳል።

ዘገባው የአልአረቢያ ነው።

@TikvahethMagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...