ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ልታስገባ ስለማሰቧ ተዘግቧል

Date:

በኬንያ የኃይል ፍላጎት የጨመረ ሲሆን ሊያጋጥም የሚችልን የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ለማስገባት እንዳቀደች ተነግሯል።

የኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ጆሴፍ ሲሮር ከኢትዮጵያ ተጨማሪ ከ50-100 ሜጋ ዋት ኃይል ለማስገባት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ንግግር ስለመጀመሩ ገልፀዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው አሁን የተጠየቀው ጥያቄ እስካሁን እየገባ ካለው የ200 ሜጋ ዋት በተጨማሪ መሆኑን ሲገልፁ ኃይሉ የተፈለገው ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ባለበት ከምሽት 12 ሰዓት እስከ ምሽት 4 ሰዓት ድረስ መሆኑን ገልፀዋል።

በ2024 የኬንያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደገለፀው ኬንያውያን ከሚጠቀሙት ዕለታዊ የኃይል ፍጆታ ውስጥ 11 በመቶው ከኢትዮጵያ እንደነበር መግለፁ ይታወሳል።

ኬንያ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኡጋንዳ እና ከታንዛኒያ ታስገባለች።

@tikvahethmagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...